ፋብሪካው በ10 ሺሕ ሄክታር መሬት ላይ እንደሚገነባ የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ አያይዘውም የሚገነባበት ቦታ ለስኳር ምርት ምቹ መሆኑን፣ የአፈር ሁኔታውን፣ የአየር ንብረቱን እንዲሁም ውኃ ገብነቱን በማጥናት ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
እንዲሁም ቦታው አስቀድሞ በልማት ባንክ ሥር እንደነበር እና ኢትዮ ስኳር በጨረታ አሸንፎ ከልማት ባንከ እንደገዛው ጠቁመው፣ ለእርሻ ሥራ አስፈላጊ የሆኑ እንደ ትራክተር እና ዶዘር የመሳሰሉ ከ100 በላይ ሜካናይዘድ የእርሻ መሣሪያዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።